ሕግ ያልወጣለት የሰው ሠራሽ አስተውሎት ሐሰተኛ መረጃ እና የመራጮች ተጋላጭነት

  • ቪኦኤ ዜና

ሰው ሠራሽ አስተውሎት (ኤአይ)

በዩናይትድ ስቴትስ፣ በመጪው ኅዳር ወር በሚካሔደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ፣ ለፖለቲካ ዓላማ በሰው ሠራሽ አስተውሎት ሊፈበረኩ የሚችሉ ሐሰተኛ ምስሎችንና ቪዲዮዎችን ለማስቆም የሚያስችል የሕግ ማኅቀፍ አለመኖር የምርጫ ሒደቱ ስጋት ኾኗል፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ሕግ ያልወጣለት የሰው ሠራሽ አስተውሎት ሐሰተኛ መረጃ እና የመራጮች ተጋላጭነት

ይኸውም፣ ሰው ሠራሽ አስተውሎትን ተጠቅመው የተሳሳተ መረጃ በመፈብረክ፣ ተፎካካሪ ፖለቲከኞችን የሚጠቅሙ ወይም የውጭ መንግሥታትን ጥቅም የሚያራምዱ ሐሰተኛ መረጃዎችን ለሚያሰራጩ ችግር ፈጣሪዎች መራጮችን ተጋላጭ ማድረጉ ነው።

የአሜሪካ ድምፅ ዘጋቢ ኢቫና ፒድቦርስካ፣ እ.አ.አ በ2024 ኅዳር ወር በሚካሔደው ምርጫ፣ የሰው ሠራሽ አስተውሎትን አጠቃቀም በሚመለከት ያደረሰችንን ዘገባ፣ ስመኝሽ የቆየ ታቀርበዋለች።