በምሥራቃዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ ከሠላሳ በላይ ሠዎች ተገደሉ

  • VOA

ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ

በምሥራቃዊ ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ውስጥ በምትገኘው ሉሃንጋ መንደር ዛሬ ቢያንስ 30 ሲቪሎች መገደላቸው ተነገረ።

አባዛኛዎቹ ሰለባዎች ሁቱዎች መሆናቸውን የገለፁት ባለሥልጣናት፣ ግድያውን የፈፀው አንድ የኛንደ ጎሣ የሆነ ሚሊሻ ነው ብለዋል።
በዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ ሠሜናዊው ኪቩ ክፍለሀገር ውስጥ በሚኖሩ ሁለቱ ጎሣዎች መካከል ለዓመታት ያህል ከዘለቀው ግጭት፣ ይኸኛው የቅርብ ጊዜው መሆኑ ነው።

የሠሜን ኺቩ ክልላዊ አስተዳዳሪ ጆይ ቦከለ እንደተናገሩት፣ ጥቃቱ ሉሃንጋ ውስጥ ሊቀሰቀስ የቻለው፣ ሚሊሻዎቹ መጀመሪያ በአንድ የኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ወታደራዊ ጦር ሠፈር ላይ ጥቃት በመክፈታቸው ነው።