የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ጀመረ

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት መጀመሩን አስታወቀ።

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት መጀመሩን አስታወቀ።

ተቋርጦ ለቆየበትም ጊዜ የማካካሻ ትምህርት እንደሚሰጥ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ያሬድ ማሞ ለቪኦኤ ገልፀዋል።

በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በወንጀል የተጠረጠሩ 22 ተማሪዎች በፀጥታ አካላት ቁጥጥር ሥር መዋላቸውንና ዩኒቨርሲቲውም የዲሲፕሊን እርምጃ እንደሚወስድ አመልክተዋል።

የግቢውን ፀጥታ የሚያጠናክሩ ሥራዎች እንደከናወኑም ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተከስቶ በነበረው ግጭት የአንድ ሰው ሕይወት እጥፋቱንና 12 ተማሪዎች መቁሰላቸውን ቀደም ሲስ ዘግበን ነበር።

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ጀመረ