በድሬዳዋ ግጭት ተከሰተ

ድሬዳዋ

ከትናንት አመሻሹ ጀምሮ ድሬዳዋ ላይ ግጭት ተከስቷል፤ ግጭቱ እስከዛሬ ከሰዓት የዘለቀ ነበር፡፡ በግጭቱ የሞቱና የከፋ ጉዳት የደረሰበት ባይኖርም ቀላል የአካል ጉዳቶችና የንብረት ውድመቶች መከሰታቸው ግን ሪፖርት ተደርጓል፡፡

ከትናንት አመሻሹ ጀምሮ ድሬዳዋ ላይ ግጭት ተከስቷል፤ ግጭቱ እስከዛሬ ከሰዓት የዘለቀ ነበር፡፡ በግጭቱ የሞቱና የከፋ ጉዳት የደረሰበት ባይኖርም ቀላል የአካል ጉዳቶችና የንብረት ውድመቶች መከሰታቸው ግን ሪፖርት ተደርጓል፡፡

የከተማዋ አስተዳደርና የሐይማኖት አባቶች ግጭቱ በድሬዳዋ ላይ የብሄርና የሐይማኖት ግጭት እንዲነሳ የሚፈልጉ የጥፋት ኃይሎች ያቀነባበሩት ነው ይላሉ፡፡

ትናንት ምሽት ላይ ቤተክርስትያን ላይ ጥቃት ተፈጽሟል ተብሎ መነገሩ ለችግሩ መባባስ ትልቅ አስተዋፅዖ የነበረው ሲሆን ቤተክርስትያኗ ግን ምንም ጉዳት አልደረሰባትም ብለዋል የሐይማኖት አባቶች፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

በድሬዳዋ ግጭት ተከሰተ

Your browser doesn’t support HTML5

በድሬዳዋ ግጭት ተከሰተ