የመላው አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ እና ሠማያዊ ፓርቲ የለገጣፎ፣ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር የእምነት ነፃነትን በመጣስ ቤተ ክርስቲያን አፍርሷል ሲል ከሰሰ፡፡
አዲስ አበባ —
የመላው አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ እና ሠማያዊ ፓርቲ የለገጣፎ፣ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር የእምነት ነፃነትን በመጣስ ቤተ ክርስቲያን አፍርሷል ሲል ከሰሰ፡፡
የከተማው አስተዳደር ከንቲባ በበኩላቸው ሕገወጥ ግንባታና የመሬት ወረራን ሊያቆም ነው ሲሉ ይናገራሉ፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ እና መኢአድ
ሁለቱ ፓርቲዎች ከትናንት በስቲያ በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ያሰራጩት ጽሑፍ በሕገ መንግሥቱ የተቀመጠውን የእምነት ነፃነት በመጣስ ለገጣፎ የተፈጸመውን፣ የቤተ ክርስቲያን ማፍረስ ተግባር አጥብቀን እንቃወማለን የሚል ርዕስ ያለው ነው፡፡
አክሎም በአጠቃላይ ዛሬ በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት በ1987 ዓ.ም በወጣው ሕገ መንግሥት፣ መንግሥት በሀይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም የሚለውን ድንጋጌ ይጥሳል ይላል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
መንግሥት የእምነት ነፃነት በመጣስ “ቤተ ክርስቲያን አፍርሷል” ሲሉ ፓርቲዎች ገለፁ