አቶ ለማ መገርሳ ዋሽንግተን ዲሲ መግባታቸው ተገለፀ

  • ቪኦኤ ዜና

የኢትዮጵያ የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ

የኢትዮጵያ የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ ዛሬ ዋሽንግተን ዲሲ መግባታቸውን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ባወጣው ዘገባ መሰረት የአቶ ለማ የአሜሪካ ጉዞ ዓላማ በሁለቱ ሃገሮች መካከል ባለው የመከላከያ ትብብር ላይ ለመነጋገር ነው።

የአቶ ለማ መገርሳን የዩናይትድ ስቴትስ ቆይታ አስመልክቶ ዘርዘር ያሉ መረጃዎችን ለማግኘት ና እራሳቸውንም አግኝተን ለማነጋገር እየጣርን ነን።

ተጨማሪ ባገኘን ጊዜ ይዘን እንመለሳለን።