መቀሌ —
በትግራይ ክልል በሚገኝ የኤርትራ ስደተኞች ካምፕ አንዲት ስደተኛ በኮሮናቫይረስ መያዟ ተገለፀ። የክልሉ ጤና ቢሮ እንደገለፀው በዓዲ ሓሩሽ በተባለ ስደተኛ ካምፕ ውስጥ የ16 ዓመት ስደተኛ በቫይረሱ ተይዛለች ብልዋል።
የፌዴራል መንግሥት የስደተኞችና የስደት ተመላሾች ኤጄንሲ በበኩሉ በፌዴራሉ መንግሥት በሚመለከታቸው መሥሪያ ቤት በይፋ በስደተኞች ካምፕ ላይ በኮሮና የተያዘ ሰው እንዳለ የተገለፀ ነገር የለም ሆኖም ግን በስደተኞች መጠለያ ቫይረሱ ለመከላከል ከገባም ለመቆጣጠር እየተሰራ ነው ብለዋል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
ኮቪድ-19 በትግራይ ክልል በሚገኝ የኤርትራ ስደተኞች ካምፕ