አቶ ታዬ ደንዳአ በቀረበባቸው ክስ ላይ የጠየቁት ማሻሻያ ውድቅ ተደረገ

Your browser doesn’t support HTML5

አቶ ታዬ ደንዳአ በቀረበባቸው ክስ ላይ የጠየቁት ማሻሻያ ውድቅ ተደረገ

የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ደ’ኤታ አቶ ታዬ ደንደኣ፣ ዛሬ ማክሰኞ፣ በፌደራል ፍርድ ቤት ቀርበው በተመሠረተባቸው ክስ ላይ የእምነት ክሕደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።

የአሜሪካ ድምፅ ያናገራቸው የአቶ ታዬ ጠበቃ አቶ የኋላእሸት ታምሩ፣ ክሱን “ወንጀል አይደለም” ሲሉ መቃወማቸውንና እንዲሻሻልም መጠየቃቸውን ገልጸዋል፡፡

ኾኖም ችሎቱ፣ ተቃውሞውንና የጠየቁትን ማሻሻያ መርምሮ፣ “ክሱን ለማሻሻል የሚያስችል የሕግ አግባብነት የለውም፤” በማለት ወድቅ ማድረጉን ጠበቃው አስረድተዋል፡፡