የእነአቶ ጃዋር መሀመድ የፍ/ቤት ውሎ

ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡት አቶ ጃዋር መሀመድና ሌሎች አሥራ አራት ተጠርጣሪዎች ጉዳያቸውን በሚመለከቱት ዳኛ ገለልተኛነት ላይ ጥያቄ ማንሳታቸውን ከጠበቆቻቸው አንዱ አቶ ቱሊ ባይሳ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።

ጠበቃው እንዳሉት፤ ተጠርጣሪዎቹ “ችሎቱን እየመሩ ያሉት ዳኛ ገለልተኛ፣ ሚዛናዊና ፍትኀዊ ስለመሆናቸው እንጠራጠራለን” ሲሉ ባለ ሰባት ገፅ ማመልከቻ አስገብተዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የእነአቶ ጃዋር መሀመድ የፍ/ቤት ውሎ