ጽንፈኛ የአመጽ መልክቶችን በመግታት ላይ ያተኮረዉ የአዲስ አበባዉ ጉባኤ

  • እስክንድር ፍሬው

Your browser doesn’t support HTML5

ጽንፈኛ የአመጽ መልክቶችን በመግታት ላይ ያተኮረዉ የአዲስ አበባዉ ጉባኤ


ጉባኤዉን በጋራ ያዘጋጁት የአሜሪካ የዓለም ተራድኦ ድርጅት USAID የአሜሪካ የመከላከያ ስጋት ቅነሳ ኤጄንሲ የአሜሪካ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና የቅርብ ምስራቅና ደቡብ ኢስያ እስትራቴጂክ ጥናት ማእከል ናቸዉ።

ከየካቲት 16 እስከ 20 በአዲስ አበባ የተካሄደዉ አዉደ ጥናት ጽንፈኛ መልክቶችን መግታት ላይ ያተኮረ መሆኑ ታዉቋል። በተለይ በአፍሪቃ ቀንድ አልሸባብና አልቃይዳ ጽንፈኛ የአመጽ መልክቶችን በማስተላለፍ በስም የተጠቀሱት ድርጅቶች ናቸዉ።

በአፍሪቃ እስትራቴጂክ ጥናት ማእከል፣ የተሻጋሪ ስጋቶችና ጸረ ሽብር ኤክስፕርት Benjamin P. Nickels በአፍሪቃ ቀንድና በሌሎች አካባቢዎች ለጽንፈኝነት አመጽ መፈጠር የተለያዩ ምክንያቶች እንዳሉ ገልጸዋል። ከእነዚህም መካከል ከአስተዳደር ጋ በተያያዘ የሚፈጠሩ ችግሮች፣ ድህነት እና በቂ ሥራ ያለመኖርን እንደምሳሌ ጠቅሰዋል።
ከእስክንድር ፍሬዉ ዘገባ ዝርዝሩን ያድምጡ።