የኣፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር 6ኛ ቀን ውሎ

አፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር

በአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ትላንት በቅድሚያ የተጫወቱት የ A ምድቦቹ አስተናጋጅ ኢኳቶሪያል ጊኒና ቡርኪና ፋሦ ያለግብ ዜሮ ለዜሮ ተለያይተዋል።

ቀጥለው የተጋጠሙት የዚሁ ምድብ ቲሞች ኮንጎ እና ጋቦን ነበሩ። በኮንጎ አንድ ለዜሮ አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

ዛሬ በሰባተኛው ቀን ቱኒዝያ ዛምቢያን ኡሁለት ለአንድ ቀጥታለች።

ፍልሚያው ነገና ከነገ በስቲያ ይቀጥላል። ቅዳሜ ዕለት በካሜሩንና ጊኒ መካከል የሚደረገውን ጨዋታ በዋና ዳኝነት እንዲመሩ ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል አርቢትር በአምላክ ተሰማ መመደባቸው ተገልጿል።

Your browser doesn’t support HTML5

የኣፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር 6ኛ ቀን ውሎ