"ኢትዮጵያ የጦርነት ወቅት የኢኮኖሚ ፖሊሲ ያስፈልጋታል"

Your browser doesn’t support HTML5

"ኢትዮጵያ የጦርነት ወቅት የኢኮኖሚ ፖሊሲ ያስፈልጋታል"

በኮቪድ-19 ወረርሽኝና በሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል ያለውን ጦርነት በማስተናገድ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ፣ የምጣኔ ሀብት ይዞታዋ የቃኙት ዶ/ር አክሎግ ቢራራ ኢትዮጵያ የጦርነት ወቅት የምጣኔ ሀብት ፖሊሲን መከተል አለባት ይላሉ፡፡

የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ዶ/ር አክሎግ "አሁን ያለው የምጣኔ ሀብት ሁኔታ የዛሬ ሦስት ዓመት በፊት ከነበረው በጣሙን ይለያል" ይላሉ፡፡

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ፣ ላላፉት 30 ዓመታት፣ በዓለም ባንክ ውስጥ በተለያዩ ኃላፊነቶች ያገለገሉ ሲሆን፣ በስተመጨረሻው ያገልግሎት ዘመናቸው፣ በባንኩ የበላይ አማካሪ ሆነው ሠርተዋል፡፡

አሁን በጡረታ ላይ የሚገኙ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ሲሆኑ፣ ጡረታ ከወጡም በኋላ የኢትዮጵያ ውሃዎች ጉዳዮች መማከርት ጉባኤና የውይይት መድረክ ፕሬዚዳንት እንዲሁም የኢትዮጵያ ግሎባል አልያንስ የቦርድ አባል ናቸው፡፡