ኢትዮጵያ ከቁም እንስሳት ሃብቷ ተጠቃሚ እንድትሆን ላኪዎችን የሚያበረታቱ አስራሮችን መተግበር እንደሚገባት ተገለጸ

ለመጀመሪያ ጊዜ የቁም እንስሳት ወጪ ንግድ በባቡር ከአዳማ ወደ ጁቡቲ ማጓጓዝ መጀመሩን የኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት ሃላፊዎች በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ ከቁም እንስሳት ሃብቷ ተጠቃሚ እንድትሆን ላኪዎችን የሚያበረታቱ አስራሮችን መተግበር እንደሚገባት ተገለጸ

ለመጀመሪያ ጊዜ የቁም እንስሳት ወጪ ንግድ በባቡር ከአዳማ ወደ ጁቡቲ ማጓጓዝ መጀመሩን የኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት ሃላፊዎች በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡ ይህም የሃገሪቱን የወጭ ንግድ ግኝት ከፍ ለማድረግ እንደሚያስችል የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስትር ካሳሁን ጎፌ ገልጸዋል፡፡

የምጣኔ ሃብት ባለሙያው አቶ ሚልዮን ክብረት በበኩላቸው ሃገሪቱ ከቁም እንስሳት ሃብቷ ተጠቃሚ እንድትሆን ላኪዎችን የሚያበረታቱ ተጨማሪ አስራሮችን መተግበር እንደሚገባት ተናግረዋል፡፡