ብሪታኒያ የፍልሰተኞችን ቁጥር ለመቀነስ የጣሊያንን አካሄድ እንዳትከተል የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ጥሪ አቀረቡ

  • ቪኦኤ ዜና

የእንግሊዝ ቻናል የማቋረጥ ሙከራ ከከሸፈ በኋላ የስደተኞች ጀልባ በዚህ መልኩ ተጎድቶ ይታያል፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ብሪታኒያ የፍልሰተኞችን ቁጥር ለመቀነስ የጣሊያንን አካሄድ እንዳትከተል የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ጥሪ አቀረቡ

ብሪታኒያ ወደ ሀገሯ ከፈረንሳይ ጋር በሚያገናኛት የአትላንቲክ ውቂያኖስ ወሽመጥ “ኢንግሊሽ ቻነል” በኩል የሚያቀኑትን በርካታ ፍልሰተኞች ለመቀነስ ጣሊያን የተጠቀመችበትን መንገድ ሥራ ላይ እንዳታውል የሰብዓዊ መብት ቡድኖች አሳሰቡ፡፡ የሰብዓዊ መብት ቡድኖቹ ጥሪውን ያቀረቡት የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚንስትር ኪር ስታርመር ጣሊያን ሜዲትራኒያን ባሕርን እያቋረጡ የሚገቡ ፍልሰተኞችን በመከታተል ረገድ ስላገኘችው ስኬት በይበልጥ ለመረዳት በዚህ ሳምንት ወደ ሮማ ማቅናታቸውን ተከትሎ ነው፡፡

ሄንሪ ሪጅዌል ከለንደን ያስተላለፈውን ዘገባ ነው፡፡