ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ ሰኔ 26/2008 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ በሙሉዓለም አዳራሸ ሊያደርገው የነበረውን ሕዝባዊ ስብሰባ ለሌላ ጊዘ ማስተላለፉን የፓርቲው አመራር አስታውቋል፡፡
አዲስ አበባ —
Your browser doesn’t support HTML5
ሰማያዊ ፓርቲ የባሕር ዳር ስብሰባውን አስተላለፈ
ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ ሰኔ 26/2008 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ በሙሉዓለም አዳራሸ ሊያደርገው የነበረውን ሕዝባዊ ስብሰባ ለሌላ ጊዘ ማስተላለፉን የፓርቲው አመራር አስታውቋል፡፡
በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋሉት የፓርቲው አባላትና ሌሎቹም ከአንድ ሰው በስተቀር አሁንም አልተለቀቁም፡፡
ኮሚቴው ስብሰባውን ለማስተላለፍ የወሰነው በክልሉ መስዳድር ዕውቅና ያገኘውን ይህንን ህዝባዊ ስብሰባ የፀጥታ ዘርፉ አላውቅም በማለቱና ቅስቀሳ ሲያካሂዱ የነበሩትን የፓርቲውን አባላት በቁጥጥር ሥር ካዋለ በኋላ የተፈጠረውን አጠቃላይ ሁኔታ በመገምገም እንደሆነ አቶ ነገሠ አስረድተዋል፡፡
በቂጥጥር ሥር የዋሉትን ሰዎች ፖሊስ ዛሬ - ቅዳሜ ቃላቸውን ተቀብሎ ከመካከላቸው አንድ ሰው መፍታቱ ታውቋል፡፡
በቁጥጥር ሥር ያሉት አሥር ሰዎች በባህር ዳር ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ እሥር ላይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
ዛሬ ከረፋዱ ጀምሮ ፖሊስ ሙሉዓለም አዳራሽን ከብቦ እንደነበር አቶ ነገሠ ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡