በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሰዎችን በመግደል የተጠረጠሩ ተያዙ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ማንዱራ ወረዳ ሰባት ሰዎችን በመግደል የተጠረጠሩ 14 ግለሰቦችን መያዙን የክልሉ ፀጥታና ሰላም ግንባታ ቢሮ አስታወቀ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ጥቃቱን የፈፀሙበት ጠበንጃና ቀስቶች፤ መያዙን ነው የቢሮው ኃላፊ የገለፁት፡፡

በሌላ በኩል የቀበሌው ነዋሪዎች ሌላ ጥቃት ሊፈፀምብን ይችላል በሚል ስጋት ወደ አማራ ክልል እየሄዱ መሆናቸው ተነግሯል::

ክልሉ ሁኔታውን ለማረጋጋት ከአማራ ክልል አመራር ጋር ለመወያየት ማቀዱን አስታውቋል፡፡

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሰዎችን በመግደል የተጠረጠሩ ተያዙ