ራያ ቢራ ፋብሪካ ገበሬዎችን በመኖ እያገዘ ነው

  • ግርማይ ገብሩ

ራያ ቢራ ፋብሪካ ላካባቢው ገበሬዎች የቤት እንስሳት መኖ በማቅረብ ላይ መሆኑ ግርማይ ገብሩ የላካቸው የፎቶ መድብል

ራያ ቢራ ፋብሪካ በማይጨው ከተማ አቅራቢያ ላሉ ገበሬዎች እስካሁን ከሦስት ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ተረፈ-ምርት በእርዳታ መስጠቱን አስታውቋል፡፡

በማይጨው ከተማ በአንድ ቢሊዮን ሰባት መቶ ሚሊዮን ቢሊዮን ብር መዋዕለ-ነዋይ የተቋቋመው የራያ ቢራ ፋብሪካ በደቡብ ትግራይ ያጋጠመውን የእንስሣት መኖ እጥረት ለመቋቋም የፋብሪካውን ተረፈ-ምርት ለገበሬዎች በነፃ እያከፋፈለ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ፋብሪካው እስካሁን ሦስት ሚሊዮን ሦስት መቶ ሺህ ብር የሚገመት እርዳታ የሰጠ ሲሆን በዚህ ዓመት ሃያ ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ተረፈ-ምርት ለገበሬዎቹ በነፃ ለመስጠት አቅዷል።

ግርማይ ገብሩ ገበሬዎቹን አነጋግሮ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ይድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ራያ ቢራ ፋብሪካ ገበሬዎችን በመኖ እያገዘ ነው /ርዝመት - 5ደ28ሰ/