ተፈጥሮንም ትውልድንም እየታደገ ያለው የጣና ሐይቁ አቤል ጫኔ

Your browser doesn’t support HTML5

ተፈጥሮንም ትውልድንም እየታደገ ያለው የጣና ሐይቁ አቤል ጫኔ

አቤል ጫኔ የባሕር ዳር ከተማ ወጣቶች በጣና ሐይቅ ዙሪያ ሥራ እንዲፈጥሩ ዕድሉን ያመቻቻል፤ በሐይቁ ዙሪያ የውኃ ዳር መንገዶችንና መዝናኛዎችን በመሥራት ከተማዋን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ይጥራል፤ በሐይቁ የዓሣ ሀብት ላይ ርባታ እና ምርምር የሚካሔድበት ስፍራ በማዘጋጀትና በማራባት የጣና ሥነ ሕይወታዊ ሀብት እንዲሻሻል እያደረገ ይገኛል፡፡ ለዚህ ጥረቱም የመስኩ ባለሞያዎች ምስክርነት ሰጥተዋል፤ በባሕር ዳር ከተማ፣ በበጎ ሥራቸው አዎንታዊ ተጽእኖ ለፈጠሩ ግለሰቦች

የሚሰጠውንም እውቅና ለማግኘት በቅቷል- ወጣት አቤል ጫኔ ይባላል፡፡

በጣና ሐይቅ ዙሪያ ለተሰማሩ ሠራተኛ ወጣቶች አርኣያ-ሰብ የኾነውን የወጣት አቤልን ትጋት እንዳስሳለን፡፡