“ቀውሶች እንዳይፈጠሩ አስቀድሞ መጠንቀቅ ያስፈልጋል” ጉቶሬዝ

  • እስክንድር ፍሬው

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀኃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ

በሀገራት የሚከሰቱ ቀውሶችን ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ ቀድሞውንም እንዳይፈጠሩ መስራት እንደሚያስፈልግ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀኃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ተናገሩ፡፡

በሀገሮች የሚከሰቱ ቀውሶችን ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ ቀድሞውንም እንዳይፈጠሩ መስራት ያስፈልጋል ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀኃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ተናገሩ፡፡

ዋና ፀኃፊው በአፍሪካ ሕብረት መሪዎች ጉባዔው ላይ ባደረጉት ንግግር ዓለም አቀፉ ተቋም በዚህ ላይ ተባብሮ መስራት ያስፈልገዋል፡፡

ዓለም አቀፉን ተቋም መምራት ከጀመሩ ወዲህ ለአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ንግግር ሲያደርጉ የመጀመሪያቸው ነው - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀኃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፡፡ ንግግራቸውም ከአፍሪካ ጋር በሚኖራቸው ግንኙነት እና የትብብር መስኮች ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ከአፍሪካ ጋር በጋራ ሊሠሩባቸው ካሰቡባቸው መስኮች አንዱ ደግሞ ግጭቶች ቀውስን የማስወገድ ተግባር መሆኑን አመልክተዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

“ቀውሶች እንዳይፈጠሩ አስቀድሞ መጠንቀቅ ያስፈልጋል” ጉቶሬዝ