የዓለም አትሌቲክስ ሻምፕዮና - በካታር ዶሃ

መቅደስ አበበ

ሰሎሞን በርጋ እና ሙክታር እንድሪስ

ሎሚ ሙለታ

ዛሬ በካታር ዶሃ በተጀመረው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፕዮና ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ለግማሽ ፍፅሜ እና ፍፃሜ አልፈዋል። በ17ኛው የዓለም ሻምፕዮና ለኢትዮጵያ የመጀመርያ በሆነው የሴቶች 800 ሜትር የመጀመሪያ ዙር ድርቤ ወልተጂ በተወዳደረችበት ምድብ አራት 02፡02.71 ደቂቃ በመግባት አምስተኛ ሆና አጠናቃለች። ሆኖም የዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፕዮኗ ከተሸናፊዎች ፈጣን ሰዓት ባስመዘገበ በሚለው ህግ ነገ መስከረም 17/2012 ዓ.ም ለሚካሄደው ግማሽ ፍፃሜ አልፋለች።