አዲስ መድሃኒት - ለድህረ ወሊድ የድብታ ሕመም ሕክምና

ከወሊድ በኋላ ለድብታ የተጋለጠች ወጣት ሴት

Your browser doesn’t support HTML5

አዲስ መድሃኒት - ለድህረ ወሊድ የድብታ ሕመም ሕክምና

አንዳንድ እናቶች ልጅ ከወለዱ በኋላ ለመንፈስ ጭንቀት የሚጋለጡበት ሁኔታ ይከሰታል።

ለድህረ ወሊድ የድብታ ሕመም የተጋለጡ እናቶች ከፍተኛ የስሜት መዋዠቅ፣ ጥልቅ ሃዘን፣ የበረታ ድካም፣ የጥፋተኝነት ስሜት፣ ጭንቀት እና ልጃቸውን በወጉ የመንከባከብ ችግር ጭምር ሊገጥማቸው ይችላል።

ዶ/ር አሌክስ አካሉ በዩናይትድ ስቴትስ የምግብ እና የመድሃኒቶች ቁጥጥር አስተዳደር የካንሰር ተመራማሪ

ሳምንታዊው ‘ሃኪምዎን ይጠይቁ’ ይህን ድሕረ ወሊድ የሚከሰት ሕመም ለማከም የሚረዳ አዲስ መድሃኒት ምንነት ይመለከታል።

ሞያዊ ትንታኔውን የሚሰጡን በዩናይትድ ስቴትሱ የምግብ እና የመድሃኒቶች ቁጥጥር ባለ ሥልጣን በምርምር ባለሞያነት በማገልገል ላይ የሚገኙት ዶ/ር አሌክስ አካሉ ናቸው።

ዶ/ር አሌክስ’ን ያነጋገገረው የፕሮግራሙ አዘጋጅ እና አቅራቢ አሉላ ከበደ ነው።