በቡራዩና አካባቢው የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 58 መሆኑን አምነስቲ አስታወቀ

አምነስቲ ኢንተርናሽናል

በቡራዩና አካባቢው የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 58 መሆኑን ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን እስካሁን ከየሆስፒታሉ የተሰበሰበው መረጃ በእጃቸው እንዳልደረሰ ገልጾ ቁጥሩ አምነስቲ የጠቀሰው ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።

በተለየያ መንገድ የቆሰሉ ሰዎች 300 እንደሚደርሱም ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል። ሰዎችን በመግደልና ግጭት ቀስቃሽ ድርጊቶችን በመፈፀም የተለዩ ሰዎች ከቡራዩም ከአዲስ አበባም መታሰራቸውን የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዘይኑ ጀማል ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ)

Your browser doesn’t support HTML5

በቡራዩና አካባቢው የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 58 መሆኑን አምነስቲ አስታወቀ