አምነስቲ እስራኤልን የሰብአዊ መብት አያያዝ ኮነነ

  • ቪኦኤ ዜና

እስራኤል በፍልስጥኤም ያላት የሰብአዊ መብት አያያዝ እኤአ በ1948 እስራኤል ራሷ ስትመሰረት ከነበረው የጭቆናና የበላይነት የገነነበት ስርዓት ጋር የተያያዘ ሲሆን ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አፓርታይድ ብሎ ከሚጠራው ጋር ተመሳሳይ ትርጉም ሊሰጠው የሚችል ነው ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል አዲስ ባወጣው መግለጫ አሳታወቀ፡፡

እስራኤል ግን አፓርታይድ የዘር መድልዎ መኖሩን በመግለጽ የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት የተቃወመች ሲሆን የአረብ ዜግነት ያላቸውም የእኩልነት መብትን የተጎናጸፉ ናቸው ብላለች፡፡