Your browser doesn’t support HTML5
ባለፈው ሳምንት መጨረሻ አርብ በከተማዋ በሚገኝ ትምህርት ቤት የተከሰተውን የቦምብ ፍንዳታ ተከትሎ ሥጋት የገባቸው የባሕር ዳር ከተማ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እየላኩ እንዳልሆነ ገልፀዋል፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉዓለም አቤ፣ ባለፈው አርብ በአድቬንቲስት አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተፈፀመ ጥቃት አንድ መምህርና ሁለት ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል ብለዋል።
ጥቃቱን ተከትሎ ትላንትና ዛሬ በከተማው በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ገብተው የሚማሩ ተማሪዎች ቁጥር መቀነሱን አክለው ገልጸዋል።
ሆኖም “ትምህርት ቤቶች በፀጥታ ኅይል እንዲጠበቁ ውሳኔ በመተላለፉ ወላጆች ልጆቻቸውን እንዲልኩ” በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል።