በጎንደር የጥምቀት በዓል የሽብር ጥቃት ሊያደርሱ የሞከሩ ግለሰቦች ማንነት

ፎቶ ፋይል፦ የጎንደር ጥምቀት

በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በተሳተፉበት የጎንደር የጥምቀት በዓል አከባበር ላይ የሽብር ጥቃት ሊያደርሱ የሞከሩት በህወሓት የተላኩ ግለሰቦች ናቸው፤ ሲሉ አንድ ከፍተኛ የአማራ ክልል የፀጥታ ባለሥልጣን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ጌታቸው ብርሌ ለአሜሪካ ድምፅ እንዳብራሩት ሰለ ተጠርጣሪዎቹ ማንነት የተሟላ መረጃ አለ በቅርቡም ይፋ ይደረጋል፡፡ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ኤጀንሲ ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ ጥቃት ሊፈፀሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የላካቸው አካል ማንነትን ይፋ እንደሚደረግ ጠቁሞ ነበር።

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

በጎንደር የጥምቀት በዓል የሽብር ጥቃት ሊያደርሱ የሞከሩ ግለሰቦች ማንነት