የአማራ ክልል ምክር ቤት ለሦስት ቀናት ያካሄደውን ጉባኤ ሲያጠናቅቅ አሥር ነባርና አሥራ ሁለት አዳዲስ ተሿሚዎች የተካተቱበት ካቢኔ ይፋ አድርጓል።
ዋሺንግተን ዲሲ —
የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና ምክትላቸው አቶ ብናልፍ አንዱለም በያዙት ኃለፊነት እንደሚቀጥሉ ተጠቁሟል።
እስከ ቀበሌ ድረስ ያሉ የአስትዳደር መዋቅሮች ለህዝቡ ጥያቄ ምላሽ መስጠት እንዲችሉ ተደርገው እንደሚደራጁ አቶ ገዱ ለአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል።
በክልሉ ከተካሄደው የተቃውሞ እንቅስቃሴ በኋላ የመጀመሪያ የሆነ የካቤኔ ሹም ሽር በአማራ ክልል ይፋ የተደረገው፡፡
በኦሮሚያ ክልል እንደታየው ሁሉ፣ በዚህ ክልልም አብዛኛዎቹ ተሿሚዎች አዳዲስ የሚባሉ ሰዎች ናቸው፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
Your browser doesn’t support HTML5
የአማራ ክልል አዳዲስ የካቢኔ ሹመት አስታወቀ