የአማራ ክልል ባለሥልጣናት ቀብር ሥነ ስርዓት ተፈፀመ

በቅዳሜው መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የተገደሉት የአማራ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዚዳንት የዶ/ር አምባቸው መኮንን፣ የክልሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የአቶ ምግባሩ ከበደና የፕሬዚዳንቱ አማካሪ የእዘዝ ዋሴ የቀብር ሥነ ሥርዓት፣ በባህር ዳር ቅዱስ ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን ተከናወነ።