አልሸባብ ሶማሊያ የታችኛው ጁባ ክፍለ ግዛት ጥቃት አድርሶ 12 ሰዎች ተገደሉ

  • ቪኦኤ ዜና
ሶማሊያ የታችኛው ጁባ ክፍለ ግዛት ውስጥ በሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ላይ ዛሬ ሰኞ ማለዳ የአልሸባብ ታጣቂዎች ጥቃት አድርሰው ቢያንስ አሥራ ሁለት ሰዎች ተገደሉ።

ሶማሊያ የታችኛው ጁባ ክፍለ ግዛት ውስጥ በሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ላይ ዛሬ ሰኞ ማለዳ የአልሸባብ ታጣቂዎች ጥቃት አድርሰው ቢያንስ አሥራ ሁለት ሰዎች ተገደሉ።

አልሻባባ በጥቃቱ ዒላማ ያደረገው ከኪስማዮ ከተማ ሃምሳ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ላይ መሆኑን የሶማሊያ ባለሥልጣናት ለቪኦኤ የሶማሊእና አገልግሎት ገልፀዋል።

አልሸባብ ካምፑን ወርረን ሃያ ሰባት የመንግሥት ወታደሮች ገድለናል ያለ ሲሆን የመንግሥቱ ባለሥልጣን መሰረተ ቢስ ሲሉ አስተባብለዋል።