የአፍሪካ አየር መንገዶች በኮሮናቫይረስ ውስጥ

የአፍሪካ አየር መንገዶች ከኮሮናቫይረስ ሳቢያ የተጣለው የትራንስፖርት ገደብ ካደረሰባቸው ጉዳት ለማገገም ከሦስት ዓመታት በላይ እንደሚወስድባቸው የአየር ትራንስፖርት ኢንደስትሪው ውስጥ አዋቂዎች ተናግረዋል፡፡ የዚያኑ ያክልም፣ በዓለምቀፉ ቀውስ፣ እየተንገታገተ ያለው ኢንደስትሪ፣ ራሱን በአዲስ መንገድ አደራጅቶ የተለያዩ ስልቶችን በማቀድ፣ ውጤታማ ሊሆን የሚችልበትም እድል የተከፈተለት መሆኑን የቪኦኤ ሪፖርተር አኒታ ፓወል ከጆሀንስበርግ ዘግባለች፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድን የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ አቶ ሄኖክ ሲራክ ደግሞ አየር መንገዱ የአገልግሎቱን ዘርፈ ብዙነት በማሳዳግ የቀውሱን ጊዜ በውጤታማነት እየተሸጋገረ መሆኑን ለአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው ፕሮግራም ተናግረዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

Your browser doesn’t support HTML5

የአፍሪካ አየር መንገዶች በኮሮናቫይረስ ውስጥ