ወለጋ ዩኒቨርስቲ በአፋን ኦሮሞ ተማሪዎችን አስመረቀ

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ አራት ተማሪዎችን በአፋን ኦሮሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በሦስተኛ ዲግሪ አስመረቀ

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ አራት ተማሪዎችን በአፋን ኦሮሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በሦስተኛ ዲግሪ ማስመረቁን አስታወቀ።

በዩኒቨርሲቲው የምሩቃኑ መምህርትና የጥናት አማካሪ ዶ/ር አሊማ ጅብሪል እንዳሉት ተማሪዎቹን ለመጀመሪያ ጊዜ በአፋን ኦሮሞ በሦስተኛ ዲግሪ ማስመረቃችን አይረሴና ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።

ከተመራቂዎቹ መካከል ዶ/ር መርጋ ገመዳ ራዲዮ ይሰብራል ሲባል የነበረውን አፋን ኦሮሞ በሦስተኛ ዲግሪ ደረጃ ለመማር መብቃታቸው ለእርሳቸውም ሆነ ለቋንቋው ተናጋሪዎች ትልቅ ድል ነው ብለዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ወለጋ ዩኒቨርስቲ በአፋን ኦሮሞ ተማሪዎችን አስመረቀ