የአዲግራት ዩኒቨርስቲ ተማሪ ሞት በሌሎች ዩኒቨርስቲዎች ግጭት ቀስቅሷል

የአዲግራት ዩኒቨርስቲ ከፌስቡክ ላይ የተገኘ ፎቶ ነው

በአዲግራት ዩኒቨርስቲ በተማሪዎች መካከል በአንድ ዘፈን ምክኒያት ቡድን የለየና ብሔርን ያማከለ ግጭት ተነስቶ የአንድ ሰው ሕይወት መጥፋቱን ተማሪዎችና ባለሥልጣናት አስታወቁ። ግጭቱ ወደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች ተዛምቷል ተብሏል።

Your browser doesn’t support HTML5

የአዲግራት ዩኒቨርስቲ ተማሪ ሞት በሌሎች ዩኒቨርስቲዎች ግጭት ቀስቅሷል

በዩኒቨርስቲውም አንድ ከምእራብ ጎጃም ደጋ ዳሞት ለትምህርት የሄደ ወጣት ከግጭቱ ጋር በተያያዘ ህይወቱ ማለፉን የአማራ ክልል አስታውቋል።

ይህን ተከትሎም በወልዲያ፣ ጎንደርና አምቦ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎች ተቃውሞ እያሰሙ መሆኑን ተማሪዎች ተናግረዋል።

ተማሪዎቹ፤ ጉዳዩ ወደ ለየለት የብሔር ግጭት እያመራ በመሆኑ በአስቸኳይ እልባት ሊያገኝ ይገባል ይላሉ። የአዲግራት ዩኒቨርስቲ ቃል አቀባይ “እንደሚወራው አይደለም ሁኔታዎች ተረጋግተዋል ለግጭቱ ምክኒያት ናቸው የተባሉ ተማሪዎች በቁጥጥ ስር ውለዋል።” ብለዋል።

በትናንትናው ዕለት የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶችን ቀን ያከበረው የሰብዓዊ መብት ጉባዔ (ሰ.መ.ጉ)በኢትዮጵያ ብሔር ተኮር ግጭቶችና መፈናቅሎች በመባባሳቸው ሁኔታው ከመቼውም በላይ አስጊና አሳሳቢ ነው ሲል አስታውቋል።