የኑሮ ውድነት እና የሰላም ዕጦት ያሳሰባቸው የዐዲስ አበባ ነዋሪዎች የዐዲስ ዓመት ጥሪ

Your browser doesn’t support HTML5

የኑሮ ውድነት እና የሰላም ዕጦት ያሳሰባቸው የዐዲስ አበባ ነዋሪዎች የዐዲስ ዓመት ጥሪ

በተጠናቀቀው ዓመት ያጋጠሙ የኑሮ ውድነት እና የሰላም ዕጦት ችግሮችን መቅረፍ፣ በዐዲሱ ዓመት ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው፣ በዐዲስ አበባ ከተማ አስተያየታቸውን የሰጡን ነዋሪዎች ጠየቁ፡፡

የሸኘነው 2015 ዓ.ም. ፈተናዎች የበዙበት እንደነበር ያወሱት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ ፈተናውን ለመቀነስ እና የሚያስከትለውን መከራ ለመቅረፍ፣ ከመንግሥት ጀምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሓላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡

በበዓሉ ግብይት እና ድባብ ላይ ያላቸውን ትዝብትም አጋርተውናል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ዘገባ ይከታተሉ።