ዜና እረፍት

የህግ ባለሙያ እና ጠበቃ አብዱልጃባር ሁሴን

የህግ ባለሙያ እና ጠበቃው አብዱልጃባር ሁሴን ትናንት፤ ነሃሴ 5/2013 ማረፋቸውን ከቤተሰባቸው የተገኘ መረጃ አመለከተ።

የአቶ አብዱልጀባር አስከሬን ቀብር ዛሬ አዳማ ከተማ ውስጥ ተፈፅሟል። የህግ ባለሙያ እና ጠበቃ አብዱልጀባር ሁሴን ትናንት በአዳማ ከተማ ገንደ ገዳ የሚባል ቀበሌ ውስጥ ወድቀው መገኘታቸውንና ህይወታቸው ማለፉን ወንድማቸው አቶ ሱልጣን ሁሴን ገልፀዋል።

ወንድማቸው ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ ከቤት ወጥተው አንድ ሰዓት አካባቢ ማረፋቸውን ነው የሰማነው ብለዋል አቶ ሱልጣን።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ዜና እረፍት