ድርጅቱ ከዩክሬን የተላከው እህል ኢትዮጵያ ገብቷል አለ

  • ቪኦኤ ዜና

ድርጅቱ ከዩክሬን የተላከው እህል ኢትዮጵያ ገብቷል አለ

በዩክሬኑ ጦርነት ሳቢያ በሩሲያ በተዘጋው የጥቁር ባህር የዩክሬን እህል እንዲወጣ ለማስቻል እየተንቀሳቀሰ በሚገኘው አካል አማካይነት ከዩክሬን የተላከው የመጀመሪያው የእህል እርዳታ ኢትዮጵያ በሚገኘው ዋነኛው የእህል መጋዘናችን ገብቷል ሲል የዓለም ምግብ ድርጅት ዛሬ አስታውቋል፡፡

ድርጅቱ በትዊተር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት እህሉ አንድ ወር ለሚሆን ጊዜ በድርቅና በግጭት የተፈናቀሉ 1.5 ሚሊዮን ሰዎችን ለመርዳት ይውላል ብሏል፡፡