የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ "ሕግ የማስከበር ዘመቻ ሲል" በጠራው ዘመቻ ከ4 ሺሕ 500 በላይ ሰዎችን ሰሞኑን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንም የፌዴራል መንግሥትና የክልሉ የፀጥታ ኃይሎች “በተቀናጀ መንገድ የሕግ በላይነትን ማስከበር” በሚል ባለፉት ጥቂት ቀናት መውሰድ በጀመሩት እርምጃ ጋዜጠኞችና የማኅበረሰብ አንቂዎችን ጨምሮ በርካታ ሰዎች መታሰራቸውን ገልጿል።
Your browser doesn’t support HTML5
የተወሰኑት ታሳሪዎች በቤተሰቦቻቸው የተጎበኙና በተለያየ የጊዜ መጠን ወደ ፍርድ ቤት የቀረቡ ቢሆንም በርካታ ታሳሪዎች ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጭ መታሰራቸውን፣ ፍርድ ቤት ያለመቅረባቸውን፣ በቤተሰብ አለመጎብኘታቸውን መመልከቱን ኢሰመኮ ጨምሮ ገልጿል።
“የሕግ የበላይነትን የማስከበር ሂደት ሰብዓዊ መብቶችን በጣሰ መልኩ መሆን የለበትም” ሲሉ የኮሚሽኑ የሕግና ፖሊሲ ጉዳዮች ኃላፊ ወ/ሮ ታሪኳ ጌታቸው አሳስበዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5