የብራዚል ፕሬዚዳንት በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተገለፀ

  • ቪኦኤ ዜና

የብራዚል ፕሬዚዳንት ጄይር ቦርሳኖናሮ

የብራዚል ፕሬዚዳንት ጄይር ቦርሳኖናሮ በምርመራ ኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው ተገለፀ።

ፕሬዚዳንቱ የትኩሳትና የህመም ስሜት እንደነበራቸው ሲገለፅ ቫይረሱ ለቫይረሱ መጋለጣቸው ተጠቁሟል።

የብራዚል ኮቪድ-19 የደቀነውን አደጋ በማጣጣል ሲናገሩ እንደነበረ፣ በአንድ ወቅትም ለደጋፊዎቻቸው ሲናገሩ ስፖርተኛ እንደነበሩ አስታውሰው ቫይረሱ ቢይዘኝም ከምንም አልቆጥረው ሲሉ ተሰምተው።

ወረርሽኙኑም በመናቃቸውም ቫይረሱን ለመከላከል የሚመከሩ መንገዶችን የሚያደንቅፍ ተግባር ፈጽመዋል፣ ህዝቡ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል መጠቀም ግዴታ የሚያደርግ ህግ እንዳይወጣም አሰናክለዋል ተብሏል።