አፍሪካ ነክ ርዕሶች

አፍሪካ ህብረት

ደቡብ ሱዳን ለአፍሪካ ኅብረት አባልነት ማዋጣት ያለባትን ገንዘብ ባለመክፈሏ ድርጅቱ ድምፅ የመስጠት መብቷን አግዷል። ሀገሪቱ አልከፈለችም የተባለው መዋጮ 9 ሚልዮን 191 ሺህ ዶላር መሆኑን ጀምስ ባቲ ባጠናቀረው ዘገባ ገልጿል።

በሌላ ዜና ደግሞ ከአፍሪካ የበዙ ስደተኞች በሚነገረው ዩጋንዳ ኮንጎ ዲሞክራስያዊት ሪፑብሊክ ውስጥ ከሚካሄደው ግጭት በቅርቡ የሸሹ 4ሺህ ሰደተኞችን ተቀብላለች። ዩጋንዳ 1ሚልዮን 4መቶ ሺህ ስደተኞችን ያስጠለለች ሲሆን አንድ ሦስተኛ የሚሆኑት ከኮንጎ የተሰደዱ እንደሆኑ ካምፓላ የምትገኘው ሪፖርተራችን ሀሊማ አቱማኒ ዘግባለች።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

አፍሪካ ነክ ርዕሶች