የአፍሪካ መከላከያ ሚኒስትሮች ስብሰባ በአዲስ አበባ ተጀምሯል

Your browser doesn’t support HTML5

የአፍሪካ መከላከያ ሚኒስትሮች ስብሰባ በአዲስ አበባ ተጀምሯል

የአፍሪካ መከላከያ ሚኒስትሮች በአዲስ አበባ ስለአህጉሪቱ ሰላምና ፀጥታ በመወያየት ላይ ናቸው፡፡

ለአህጉሪቱ የመከላከያ ሚኒስትሮች የመጀመሪያ መሆኑ የተነገረውን ይህን ስብሰባ ኢትዮጵያ እንዳዘጋጀች ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ አፍሪካ በውስብስብ የፀጥታ ችግር ዉስጥ መሆኗን ተናግረዋል።

የስብሰባው ተሳታፊዎች በተለይ የአፍሪካ ተጠባባቂ ሠራዊት ኃይል ትግበራ ወደ ኋላ መጎተት፣ አገራት “በአህጉሪቱ ለሚያጋጥሙ ችግሮች ወደ ውጭ እንዲመለከቱ አድርጓል” ይላሉ፡፡