በደራ ወረዳ “በቀጠለው ግጭት ሰባት ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል” ሲሉ ነዋሪዎች ተናገሩ

Your browser doesn’t support HTML5

በደራ ወረዳ “በቀጠለው ግጭት ሰባት ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል” ሲሉ ነዋሪዎች ተናገሩ

በኦሮሚያ ክልል ፣ሰሜን ሸዋ ዞን፣ደራ ወረዳ፣በመንግሥት ኃይሎችና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት እንደዚሁም በመንግሥት ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከመስከረም 27 ቀን 2017 ዓ/ም በቀጠለው ግጭት ሰባት ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል።

ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁት እነዚሁ ነዋሪዎች እንዳሉት የሟቾቹ አስከሬን የተገኘው ጥቅምት 2 ቀን 2017 ዓ/ም. ነው።

የአሜሪካ ድምፅ ስለጉዳዩ ካነጋገራቸው ሁለት የዞንና የወረዳ ባለስልጣናት አንዱ “ምንም ውጊያ የለም” በማለት ሲያስተባብሉ፣ ሌላው በበኩላቸው ወረዳው “ከፀጥታ ችግር ውጭ ሆኖ አያውቅም” ብለዋል።