Your browser doesn’t support HTML5
“የአፍሪካ ሀገሮች የተጫናቸው ዕዳ ኤድስን ለማጥፋት የተያዘውን ጥረት እየጎዳው ነው” ተመድ
“ከሰሐራ በታች ያሉትን የአፍሪካ ሐገሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ በይበልጥ እየተጫናቸው የሄደው የብድር እዳ ወሳኝ ለሆኑ ጸረ ኤችአይቪ አገልግሎቶች የሚውል ገንዘብ እንዳይተርፋቸው እያደረገ ነው” ሲል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸረ ኤድስ ቢሮ ያወጣው አዲስ ሪፖርት አመለከተ፡፡ የብድር ዕዳ ቀውሱ ኤድስን ለማስወገድ በሚደረጉ ጥረቶች እስካሁን የተገኙትን ውጤቶች እያደናቀፈ መሆኑን ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
ኮለምበስ ማቩንጋ ከዚምባቡዌ ዋና ከተማ ከሐራሬ ያጠናቀረው ዘገባ በቀጣዩ አፍሪካ ነክ ርዕሶች ይቀርባል፡፡