ከመስከረም 11 ጥቃት 23 ዓመታት በኋላ ሽብርተኝነት አሜሪካና ዓለምን እያንዣበበ ነው

  • ቪኦኤ ዜና

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና ምክትል ፕሬዝዳንት ካምላ ሄሪስ ከቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ፣ የቀድሞው የኒው ዮርክ ከንቲባ ማይክ ብሉምበርግ እና የሪፐብሊካን ፓርቲውን ወክለው በምክትል ፕሬዝደንትነት የሚወዳደሩት ጄዲ ቫንስ

Your browser doesn’t support HTML5

ከመስከረም 11 ጥቃት 23 ዓመታት በኋላ ሽብርተኝነት አሜሪካና ዓለምን እያንዣበበ ነው

ምክትል ፕሬዚደንት ካማላ ሄሪስ ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ጋር በመሆን አሜሪካ ምድር ላይ የተፈጸመውን አስከፊ የሽብር ጥቃት 23ኛውን ዓመት ለማክበር ተገኝተዋል። በጥር ወር የፕሬዚዳንትነቱን ቦታ የሚይዝ ማንኛውም ሰው፣ ሃሪስም ሆኑ በስነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት ተቀናቃኛቸው የቀድሞ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ፣ የተለያዩ ስጋቶች ይጠብቃቸዋል።

የቪኦኤ የዋይት ሀውስ ዘጋቢ አኒታ ፓወል የተጠለፈው አውሮፕላን ተከስክሶባቸው የወደሙት፣ ሁለቱ የቀድሞ የዓለም ንግድ ማእከል ህንጻዎች በነበሩበት “ግራውንድ ዜሮ” ተብሎ በሚጠራው ኒው ዮርክ፣ እንዲሁም በፔንስልቬንያ ግዛት ሻንክስቪል እና ከፔንታገን ተከታዩን ዘግባለች፡፡