‘በሱዳኑ ጦርነት ሁለቱም ወገኖች በሰብአዊ መብት ተጠያቂ ናቸው’ ተመድ

በሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት የተፈናቀሉ ቤተሰቦች በዑመር ኢብኑል ኸጣብ

Your browser doesn’t support HTML5

‘በሱዳኑ ጦርነት ሁለቱም ወገኖች በሰብአዊ መብት ተጠያቂ ናቸው’ ተመድ

በሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት የሚፋለሙት ሁለቱም ወገኖች በጦር ወንጀል ደረጃ ሊፈረጁ የሚችሉ ጥቃቶችን መፈጸማቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የመደበው መርማሪ ልዑክ ዛሬ ዓርብ ይፋ ባደረገው ሪፖርቱ አስታወቀ።

የዓለም ኅያላን የሲቪሎችን ደሕንነት የሚጠብቁ ሰላም አስከባሪዎችን እንዲልኩ እና የዳርፉሩ የጦር መሣሪያ ማእቀብም በመላዋ ሱዳን እንዲጸና ሐሳብ አቅርቧል።