የሪፐብሊካኑ ፕሬዝደንታዊ ዕጩ ዶናልድ ትራምፕ እና የዴሞክራቲክ ፕሬዝደንታዊ ዕጩ ምክትል ፕሬዝደንት ካማላ ሃሪስ፣ አንድ ጊዜ የሪፐብሊካኑን እጩ ሌላ ጊዜ ደግሞ የዲሞክራቱን ዕጩ በመምረጥ በሚታወቁት ግዛቶች ለማን ድምጻቸውን እንደሚሰጡ እስካሁን ያልወሰኑ መራጮችን ቀልብ ለመግዛት ጥረት በያዙበት በአሁኑ ወቅት፤ አንዱ በሌላው ላይ የተነጣጠረ የሰላ ጥቃት መሰንዘራቸውን ቀጥለዋል።
Your browser doesn’t support HTML5
መጭው 100 ቀናት ለዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ “የሞት ሽረት” ይሆናሉ ተባለ
ሁለቱ ወገኖች ከሦስት ወራት አነስ ያለ ጊዜ ብቻ ለቀረው ምርጫ በየፊናቸው በሚያካሂዱት የምረጡኝ ዘመቻ ፉክክርም ‘ይበልጥ ተጋግሞ ይቀጥላል’ ተብሎ ተጠብቋል። የአሜሪካ ድምጿ ቬሮኒካ ባልደራስ ኢግሌሲያስ የሚከተለውን ዘገባ አዘጋጅታለች።