ባይደን ወደኋይት ሐውስ ተመልሰዋል

  • ቪኦኤ ዜና

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ጆ ባይደን በዴለዌር፣ሮኾቦት ቢች በኩል ወደ ዋይት ኋውስ ሲያመሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ሰላምታ ሲሰጧቸው። ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም.

- ካማላ ሐሪስም የምርጫ ዘመቻቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል

ለኮቪድ 19 መጋለጣቸውን ተከትሎ ለአንድ ሳምንት ተገልለው የቆዩት ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ትላንት ማክሰኞ ወደ ኋይት ሐውስ ቤተ መንግሥት ተመልሰዋል፡፡

ባይደን ሙሉ በሙሉ ከእይታ ተሰውረው ይሰንብቱ እንጂ ከፕሬዚደንታዊ ምርጫ ፉክክሩ ለመውጣት ያደረጉት ውሳኔ የሳምንቱ አቢይ ዜና አድርጓቸዋል፡፡

ምክትል ፕሬዚደንታቸው ካማላ ሐሪስም በምርጫ ዘመቻ እየተዘዋወሩ መሆናቸውን አክላ የአሜሪካ ድምጹዋ አኒታ ፓወል ከኋይት ሐውስ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

Your browser doesn’t support HTML5

ባይደን ወደኋይት ሐውስ ተመልሰዋል