የኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን ዋና አስተዳዳሪን ግድያ ተከትሎ ለጸጥታ ችግሮች መፍትሔ እንዲፈለግ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ካርታ

በዐማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን የሚታዩትየጸጥታ ችግሮች እና ተያያዥ ኹኔታዎች መፍትሔ እንዲበጅላቸው፣ አባ ገዳዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እናየሃይማኖት አባቶች ጥሪ አቅርበዋል።

Your browser doesn’t support HTML5

የኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን ዋና አስተዳዳሪን ግድያ ተከትሎ ለጸጥታ ችግሮች መፍትሔ እንዲፈለግ ተጠየቀ

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አሕመድ ዓሊ፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ በታጣቂዎች መገደላቸውን ተከትሎ በነዋሪዎች ዘንድ የደኅንነት ስጋት መፈጠሩንም፣ ጥሪ አቅራቢዎቹ አመልክተዋል።

በዞኑ የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አብደላ አሕመድ፣ የዋና አስተዳዳሪው ግድያ አሁንም በምርመራ ላይ እንደሚገኝ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።