በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዳግም ግጭት አምስት ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

Your browser doesn’t support HTML5

በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዳግም ግጭት አምስት ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ ዳግም በተቀሰቀሰ የጸጥታ ችግር፣ ቢያንስ አምስት ሲቪል ሰዎች መገደላቸውን፣ የተጎጂ ቤተሰብ አባላት እና የአካባቢው ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቁ፡፡

ግጭቱ ዳግም የተቀሰቀሰው፣ በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሥር የሚገኙ አራት የዘይሴ ቀበሌዎች፣ ራሳቸውን ችለው በወረዳነት ለመደራጀት ሲያቀርቡ ከነበረው ጥያቄ ጋራ በተያያዘ እንደኾነ፣ የአካባቢው የፓርላማ ተመራጭ አቶ አብርሃም ኦላሼ ለአሜሪካ ድምፅ አብራርተዋል።

በጉዳዩ ላይ ከአካባቢው ባለሥልጣናት ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።