በሆሮ ጉዱሩ ሱሉለ ፊንጭኣ ጥቃት አራት ሰላማውያን ሰዎች እንደተገደሉ ተገለጸ

Your browser doesn’t support HTML5

በሆሮ ጉዱሩ ሱሉለ ፊንጭኣ ጥቃት አራት ሰላማውያን ሰዎች እንደተገደሉ ተገለጸ

በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሱሉለ ፊንጭኣ ወረዳ፣ ባለፈው ሰኞ በተፈጸመው ጥቃት፣ አራት ሰዎች እንደተገደሉ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የቤተሰብ አባሎች ገለጹ።

የዐይን እማኞቹ እና የሟች ቤተሰቦች፣ ጥቃቱ በመንግሥት ኃይሎች እንደተፈጸመ ቢገልጹም፣ የወረዳው አስተዳዳሪ ግን፣ “የሸኔ ታጣቂዎች ናቸው፤” ሲሉ ከሰዋል።

በጉዳዩ ላይ፣ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ዓለም ዓቀፍ ቃል አቀባይ እንደኾኑ የሚናገሩት ኦዳ ተርቢ፣ የመንግሥት ኃይሎች ሰላማዊ ሰዎችን ይገድላሉ፤ ሲሉ፣ ኃይላቸው በአካባቢው ራሱን በመከላከል ላይ እንደሚገኝ ገልጸው ክሱን አስተባብለዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።