የእሥራኤል-ሐማስ ጦርነትና የዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ ቦታ

Your browser doesn’t support HTML5

የእሥራኤል-ሐማስ ጦርነትና የዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ ቦታ

አንድ ወር ያስቆጠረውና ተጋግሎ የቀጠለው የእሥራኤል-ሐማስ ጦርነት “ችግርም መፍትኄም ያለው በሁለቱም እጅ ነው” ሲሉ እስራኤልና ኢትዮጵያ ያሉ አስተያየት ሰጭዎችና ምሁራን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ የሴማዊ ሥነ ቋንቋ ከፍተኛ መምህር ዶ/ር አንበሴ ተፈራና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኛነትና ኮምዩኒኬሽንስ መምህር ዶ/ር ጀማል መሐመድ “ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ የችግሩም የመፍትሔውም አካል ነው” ብለዋል።

ደቡብ እሥራኤልና ኢየሩሳሌም ውስጥ የሚኖሩት ወ/ሮ ፀጋ ብሩክና አቶ አትክልት ተስፋዬም የዛሬ ወር በሐማስ ከተከፈተው ጥቃት አንስቶ ችግር ላይ መሆናቸውን አመልክተዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።