መንግሥት ግጭቶችን በሰላም እንዲፈታ ፓርላማው እንዲጫነው የምክክር ኮሚሽኑ ጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

መንግሥት ግጭቶችን በሰላም እንዲፈታ ፓርላማው እንዲጫነው የምክክር ኮሚሽኑ ጠየቀ

በኢትዮጵያ፣ ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ፣ ፓርላማው፥ በመንግሥት አስፈጻሚ አካላት ላይ ጫና እንዲያደርግ፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጠየቀ፡፡

ዋና ኮሚሽነሩ ፕሮፌሰር መስፍን አርኣያ፣ የ2016 በጀት ዓመት የአራት ወራት የሥራ አፈጻጸሙን፣ ዛሬ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት፣ በማያባሩ ግጭቶች የተነሳ ሥራውን በዕቅዱ መሠረት ለማከናወን እንዳልቻለ ገልጸዋል። ኹሉም የታጠቁ ኃይሎች፣ ፊታቸውን ወደ ድርድር እንዲያዞሩም አሳስበዋል፡፡