በሶማሌ ክልል የቆሎጂ መጠለያ ጣቢያ ስድስት ሰዎች እንደተገደሉ ኢሰመኮ ገለጸ

Your browser doesn’t support HTML5

በሶማሌ ክልል የቆሎጂ መጠለያ ጣቢያ ስድስት ሰዎች እንደተገደሉ ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ በሶማሌ ክልል የቆሎጂ መጠለያ ማዕከል ውስጥ በሚገኙ ተፈናቃዮች ላይ በተፈጸመ ጥቃት፣ ስድስት ሰዎች እንደተገደሉ አስታውቋል።

የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸውና በመጠለያ ጣቢያው ከሰባት ዓመት በላይ እንዳስቆጠሩ የገለጹ ተፈናቃዮች፣ 13ሺሕ የሚደርሱ አባወራዎች፣ በአስቸጋሪ ኹኔታ ኑሯቸውን እየገፉ እንደሚገኙ አመልክተዋል፡፡

ተፈናቃዮቹ፣ ወደ ሌላ የሶማሌ ክልል ዞኖች ተዛውሮ መስፈርን እንደሚሹ ሲገልጹ፣ የሶማሌ ክልልም፣ ቆሎጂን ከተፈናቃይ ጣቢያነት ወደ ከተማነት እንደሚቀይር አስታውቋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።